ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በ2018 በጀት ዓመት አመርቂ ስራዎችን ሰርቷል-ክቡር አቶ በቀለ መንገሻ

News news
2026-07-21 05:36:28

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ 2018 በጀት ዓመት አመርቂ ስራዎችን ሰርቷል-ክቡር አቶ በቀለ መንገሻ
ሐምሌ 14 2018 (ወራ/ / / / /) የዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ገምግሞ አጽድቋል።


2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚው አቶ ተማም አርጋው ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።  የዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ በቀለ መንገሻ ዩኒቨርሲቲው በበጀት ዓመቱ በሁሉም ዘርፎች የሰራቸው ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን ገልጸዋል። አለም አቀፍ ትስስርና የአጋርነት ስራዎች እንዲሁም ዲጂታላይዜሽን ላይ  የተሰሩ ውጤታማ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተናግረዋል።


 
በየደረጃው በቡድን መንፈስ መሰራቱ ለተገኘው ውጤት ማሳያ መሆኑን ክቡር አቶ በቀለ ጠቁመዋል።
 
የዩኒቨርሲቲው ምክትል የቦርድ ሰብሳቢ / አርጋው አምበሉ በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲው ውጤታማ የሆኑ ቤተሙከራዎች መደራጀታቸው የመማር ማስተማር ስራውን ውጤታማ ማድረግ ማስቻሉን ገልጸዋል።
 
የተለያዩ ሲስተሞችን በማበልጸግ ረገድም ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን አመላክተዋል።
 
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት / ኢንጂነር ተውፊቅ ጀማል ዩኒቨርሲቲው 2018 በጀት ዓመት በመማር ማስተማር፣ በምርምር፣ ማህበረሰብ አገልግሎትና አስተዳደር ዘርፎች በብዙ ቁልፍ የውጤት አመልካቾች (KPIs) ላይ የላቀ አፈጸጸም ማስመዝገቡን ተናግረዋል።
 
ዩኒቨርሲቲው 2018 በጀት ዓመት  አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንና ዩኒቨርሲቲውን ማራኪና ምቹ የስራ ከባቢ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ስራዎች መሠራታቸውን ገልጸዋል። የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2019 በጀት ዓመት ዕቅድን ገምግሞ አጽድቋል።



ዕውቀት ለልህቀት


ወራቤ ዩኒቨርሲቲ

 

650404505_1386465686832660_2574265641495798644_n-909869.jpg photo_2026-07-21_07-14-50-823761.jpg photo_2026-07-21_07-14-51-(2)-741622.jpg photo_2026-07-21_07-14-51-(3)-332640.jpg photo_2026-07-21_07-14-51-99277.jpg photo_2026-07-21_07-14-52-(2)-913377.jpg photo_2026-07-21_07-14-52-(3)-894859.jpg photo_2026-07-21_07-14-52-(4)-943022.jpg photo_2026-07-21_07-14-52-230596.jpg