ዶ/ር ኢንጂነር ተውፊቅ ጀማል በወራቤ ከተማ አስተዳደር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሄዱ
ሐምሌ 29፣ 2018 (ወራ/ ዩ /ህ /አ /አ /ግ) የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኢንጂነር ተውፊቅ ጀማል ከማኔጅመንትና
ከካውንስል አባላት ጋር በመሆን በወራቤ ከተማ አስተዳደር ዳጤ
ወዚር 6 ቀበሌ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አካሂደዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኢንጂነር ተውፊቅ ጀማል ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሚመጣን የአየር መዛባት ለመቋቋም በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ወራቤ ዩኒቨርሲቲ እንደ ሀገር እየተካሄደ በሚገኘው አረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የሚጠበቅበትን ሀገራዊ ኃላፊነት ለመወጣት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሩ በተጠናከረ ሁኔታ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኢንጂነር ተውፊቅ ጀማል በወራቤ ከተማ አስተዳደር ለዳጤ ወዚር 6 ቀበሌ ነዋሪዎች ለምግብነት የሚያገለግሉ ችግኞችን አበርክተዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩ ላይ ለምግብነትና ለደን የሚውሉ ችግኞች ተተክለዋል።
ዕውቀት ለልህቀት
ወራቤ ዩኒቨርሲቲ